መልስ - ሱረቱ ን-ናስ እና ተፍሲሯ:
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው።
{በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ። 1 * የሰዎች ሁሉ ንጉሥ በሆነው። 2 * የሰዎች አምላክ በሆነው። 3 * ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች (ሰይጣን) ክፋት። 4 * ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው። 5 * ከጋኔኖችም ከሰዎችም (ሰይጣናት እጠበቃለሁ በል)።» 6} [ሱረቱ አን-ናስ፡ 1-6]
ተፍሲር፡
1- {በል «በሰዎች ፈጣሪ እጠበቃለሁ። 1} አንተ የአሏህ መልዕክተኛ ሆይ! እንዲህ በላቸው፦ የሰዎችን ጌታ አጥብቄ እይዛለሁ፣ ጥበቃውንም እሻለሁ።
2- {«የሰዎች ሁሉ ንጉሥ በሆነው። 2} እንዳሻው ያደርጋቸዋል፤ ከእርሱም ሌላ ባለቤት የሌላቸው በሆነው።
3- {«የሰዎች አምላክ በሆነው። 3} በእውነት የሚያመልኩት አምላካቸው፤ ከእርሱም ውጭ ለነርሱ በእውነት የሚያመልኩት አምላክ የሌላቸው በሆነው።
4- {«ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች (ሰይጣን) ክፋት። 4} በሰዎች ላይ ሹክሹክታውን ከሚወረውር የሰይጣን ክፋት።
5- {«ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው። 5} ሹክሹክታውን ወደ ሰዎች ልቦና ከሚወረውረው ሰይጣን ክፋት።
6- {«ከጋኔኖችም ከሰዎችም (ሰይጣናት እጠበቃለሁ በል)።» 6} ማለትም ጉትጎታው ሰውም ይሁን ጂኒ ከክፋቱ ለመዳን የሰዎችን ጌታ አጥብቄ እይዛለሁ፣ ጥበቃውንም እሻለሁ።